
ለኮሌጁ አሰልጣኝ መምህራን የተሰጠ የሚገኘው የInnovative Pedagogy ስልጠና በፌደራል ስራና ክህሎት ሚኒስቴር አዘጋጅነት ከፌደራል TVET ኢንስቲትዩት በመጡ የዘርፉ ባለሞያዎች እየተሰጠ የሚገኝ ሲሆን የስልጠናው ዋና ዓላማም የተለመደውን የማሰልጠኛ ስነ-ዘዴ ለማሻሻልና ጊዜው የደረሰበትን ዲጂታል ቴክኖሎጂን በመጠቀም ትምህርትና ስልጠናውን ለማዘመን ያለም ስልጠና እንደሆነም ተገልፇል::
ይህ በኮሌጁ ለ5 ቀናት የሚቆየው ስልጠናም ባለፉት 15 ቀናት አሰልጣኝ መምህራኑ በOnline ሲከታተሉት የነበረውን የ Innovative Pedagogy ስልጠና በተግባር የሚሰለጥኑበት እንደሆነው ተመላክቷል::
ስልጠናው በሀገሪቱ በሚገኙና የEASE ፕሮጀክት በሚተገበባቸው 24 ፖሊቴክኒኮች ላይ ለሚገኙ አሰልጣኝ መምህራን አየተሰጠ እንደሚገኝም ታውቋል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ
ግንቦት 11/2018 ዓ.ም
ድሬዳዋ













